ኢሳያስ ባንጫ
ደራሲና ገጣሚ ኢሳያስ ባንጫ ሶስት መጽሃፍትን ለተደራሲያን አቅርቧል። እነኚህም ስሜትና ስሌት የግጥም መድብል፣ ምናብና ምንባብ የአጫጭር ታሪኮች ስብስብ ልቦለድ እንዲሁም ሃቅና ሳቅ የግጥም መድብል መጽሃፍ ናቸው። ኢሳያስ ባንጫ የመጀመሪያ ድግሪውን በኢትዮጲያ ቋንቋና ስነጽሁፍ በ2014 አ/ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ድግሪውን ደግሞ በፍልስፍና በ2017 አ/ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያገኘ ሲሆን በተጨማሪም በዲፕሎማሲና አለም አቀፍ ግኑኝነት ከኢትዮጲያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲም ሁለተኛ ድግሪውን በ2017 አ/ም አግኝቷል። በአሁን ጊዜም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ድግሪውን በፍልስፍናን እየሰራ ነው።